Joomla TemplatesBest Web HostingBest Joomla Hosting

Home ዜና የቅርብ ዜናዎች የተፈናቃዮች፣ ከስደት ተመላሾች እና የአካባቢው ማህበረሰቦች በራስ የመተማመን፣ የአካባቢ ውህደት እና ማህበራዊ ትስስርን ማጠንከር ፕሮጀክት

የተፈናቃዮች፣ ከስደት ተመላሾች እና የአካባቢው ማህበረሰቦች በራስ የመተማመን፣ የአካባቢ ውህደት እና ማህበራዊ ትስስርን ማጠንከር ፕሮጀክት

     Strengthening of Self-Reliance (1)

ፕሮጀክቱ በአማራ ክልል አዊ ዞን በጓንጓ፣ ጃዊ እና ፋግታ ለኮማ ወረዳዎች እና በቻግኒ ከተማ አስተዳደር .. 2021 እስከ ህዳር 2024 ከቢኤምዜድ/ ከጀርመን የኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ/ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ እየተተገበረ ይገኛል፡፡

     Strengthening of Self-Reliance (5)

ከሰኔ 24/2015 እስከ መስከረም 30/2016 በፕሮጀክቱ የተከናወኑ ተግባራት በሂሳብ አያያዝ፣ በብድር አጠቃቀም እና የሥራ እቅዶች አወጣጥ እና ትግበራ ዙሪያ 347 ወጣቶች (ሴ፡199) ለሥራ ዝግጁ እንዲሆኑ ስልጠና ሰጥቷል፡፡ እንዲሁም 113 ወጣቶች (ሴ፡57) ለእያንዳንዳቸው 25ሺህ ብር በጥቅሉ ብር 2.8 ሚሊዮን የመቋቋሚያ የመነሻ ካፒታል ተሰጥቶቸዋል፡፡

     Strengthening of Self-Reliance (3)

በተጨማሪም 112 ወጣቶች (ሴ፡57) በዶሮ እና በበግ እርባታ፣በባልትና ዝግጀት፣ ካፊ እና ሱቅ ሥራዎች ዙሪያ ተሰማርተዋል፡፡ በተጨማሪም 9 ወጣቶች (ሴ፡5) በተለያዩ ተቋማት የሥራ እድል እንዲያገኙ እድሉ ተመቻችቶላቸዋል፡፡ 112 ወጣቶች (ሴ፡60) 75 ኢንተርፕራይዝ አቋቋመው ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡ በሩብ አመቱ 2.6 ሚሊዮን ብር ወጪ በአራት ወረዳዎች የወጣቶች አንድ ማዕከል አገልግሎት ግንባታ እና የቁሳቁስ ማሟላት ሥራ ተሠርቷል፡፡

     Strengthening of Self-Reliance (4)

 


Language Selection
ሶሻል ሚዲያ
FacebookTwitter
የጎብኝዎች ብዛት
Today44
Week220
All139273

Currently are 15 guests online


ምርጫ
ስለ ድረ-ገፅ ያለዎት አስተያየት ?