Joomla TemplatesBest Web HostingBest Joomla Hosting

Home ዜና የቅርብ ዜናዎች በአመልድ ኢትዮጵያ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮችን የስነ-ንጽህና፣ ንጹህ መጠጥ ውሃ እና ምግብ ችግር የመቅረፍ ፕሮጀክት 12.42 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ፤

በአመልድ ኢትዮጵያ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮችን የስነ-ንጽህና፣ ንጹህ መጠጥ ውሃ እና ምግብ ችግር የመቅረፍ ፕሮጀክት 12.42 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ፤

   ORDA Ethiopia’s Mitigate  (1)

በአገር ውስጥ ባለው ግጭት ምክንያት ከኦሮሚያ ክልል፣ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እና ከሌሎች አካባቢዎች ተፈናቅለው በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን እና ደቡብ ወሎ ዞን የሚገኙ የጃሬ፣ መካነ-ኢየሱስ እና መርሳ መጠለያ ጣቢያዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተፈናቃይ ይገኛል፡፡ የእነዚህ ተፈናቃዮች ህይወት ለመጠበቅ እና በሰሜኑ ጦርነት ወቅት የተጎዱ የማህበረሰብ ክፍሎችን ኑሮ ለማሻሻል በአመልድ ኢትዮጵያ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮችን የስነ-ንጽህና፣ ንጹህ መጠጥ ውሃ እና ምግብ ችግር የመቅረፍ ፕሮጀክት ከጀርመን ሰብዓዊ እርዳታ ድርጅት በቬልት ሁንገር ህልፈ በኩል ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ .. 2023 12,421,200 ብር በመጠለያ ጣቢያዎች ለሚገኙ 1,023 ቤተሰቦች ድጋፍ ተደርጓል፡፡

   ORDA Ethiopia’s Mitigate  (2)

   ORDA Ethiopia’s Mitigate  (4)

በተጨማሪም፤

• 150 ኩንታል የስንዴ ዱቄት፣ 15 ኩንታል ክክ እና 500 ሊትር የምግብ ዘይት 1000 በመጠለያ ጣቢያዎች ለሚገኙ ተፈናቃዮች (ጃሬ፣ መካነ-ኢየሱስ እና መርሳ) ድጋፍ ተደርጓል፤

150 ቤተሰቦች የተለያዩ አልባሳት (ብርድ ልብስ እና የስፖንጅ ፍራሽ) ተሰራጭቷል፡፡

300 ቤተሰቦች የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች (የቤት ውስጥ ቁሳቁሶች) ድጋፍ ተደርጓል፡፡

540 ቤተሰቦች 54 ኩንታል የተሻሻለ የጤፍ ዘር እና 15.79 ኩንታል የእንስሳት መኖ ዘር ተሰራጭቷል፡፡

104 በጦርነት ምክንያት ጥሪታቸውን ላጡ አርሶ አደሮች 312 የእርባታ ፍየሎች ድጋፍ ተደርጓል፡፡

እንዲሁም አንድ የምንጭ ማጎልበት ስራ በመሰራቱ በተሁለደሬ ወረዳ የሚገኙ 543 ተጠቃሚዎችን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽ ማድረግ ተችሏል፡፡

   ORDA Ethiopia’s Mitigate  (3)

   

   ORDA Ethiopia’s Mitigate  (5)

 


Language Selection
ሶሻል ሚዲያ
FacebookTwitter
የጎብኝዎች ብዛት
Today42
Week218
All139271

Currently are 66 guests online


ምርጫ
ስለ ድረ-ገፅ ያለዎት አስተያየት ?