Joomla TemplatesBest Web HostingBest Joomla Hosting

Home ዜና የቅርብ ዜናዎች መሬት ለህይዎት አማራ ፕሮጀክት

   መሬት ለህይዎት አማራ ፕሮጀክት

   Land 4 life Amhara 

በቢኤምዜድ ድጋፍ፣ በጂአይዜድ እና አመልድ ኢትዮጵያ የሚተገበረው ኃላፊነት የሚሰማው የመሬት ፖሊሲ (GPRLP) ስር የሚተገበረው ኃላፊነት ያለው የመሬት ኢንቨስትመንት አስተዳደር ፕሮጀክት ከአውሮፓ ህብረት ጋር በጋራ ፋይናንስ ይደረጋል፡፡ ልዩ ዓላማው በገጠር አካባቢዎች ድህነትንና ረሃብን ለመቅረፍ በኢኮኖሚ ኋላ የቀሩ የአማራ ክልል አካባቢዎችን መሬት የማግኘትና የኢንቨስትመንት ተጠቃሚነት በዋናነት ማሻሻል የሚል ነው።

የሚከተለው ስትራቴጂካዊ አቅጣጫ ዋና ዋና ባለድርሻ አካላትን (የመንግስት ሰራተኞችን የተመረጡ ባለሀብቶችን እንዲሁም የሲቪክ ማህበረሰብ አባላት እና የማህበረሰብ ተወካዮችን) አቅም ማጠናከር እና የመሬት የኢንቨስትመንት የቁጥጥር ማዕቀፍን ማሻሻል ነው። እንዲሁም ፕሮጀክቱ ባለፉት ዓመታት በተተገበረባቸው የአማራ ክልል ሁለት ወረዳዎች (/ኤልያስ እና ወምበርማ ወረዳዎች)-

• 28 ከደን ይዞታዎች ጋር የተያያዙ ግጭቶችን በውይይት እንዲፈቱ አድርጓል፡፡

• 56 የግል እና የወል መሬቶች የድንበር ይገባኛል ግጭቶችን በማህበረሰብ ውይይት መፍታት ተችሏል፡፡

• 8 የባሕር ዛፍ ጥላ በማሳ ላይ በሚፈጥረው ጉዳት ምክንያት የተፈጠሩ ግጭቶች ተወግደዋል፡፡

• 47 ከመሬት ውርስ እና ስጦታ ጋር የተያያዙ የፍርድ ቤት ክርክሮች እና አለመግባባቶች በማህበረሰብ ውይይት ተፈተዋል፡፡

 


Language Selection
ሶሻል ሚዲያ
FacebookTwitter
የጎብኝዎች ብዛት
Today46
Week222
All139275

Currently are 88 guests online


ምርጫ
ስለ ድረ-ገፅ ያለዎት አስተያየት ?