Joomla TemplatesBest Web HostingBest Joomla Hosting

Home ዜና የቅርብ ዜናዎች "ነባር ደኖችን በመጠበቅ እና አዳዲስ ተከላ በማካሄድ ለብዝሃ-ህይዎት መሻሻል እየሰራን ነው!”፣ አለማየሁ ዋሴ (ፒኤች.ዲ.)

"ነባር ደኖችን በመጠበቅ እና አዳዲስ ተከላ በማካሄድ ለብዝሃ-ህይዎት መሻሻል እየሰራን ነው!” አለማየሁ ዋሴ (ፒኤች..)

      biodiversity by protecting existing forests  1

አመልድ ኢትዮጵያ .. 2023 ከሚተገብራቸው 38 ፕሮጀክቶች መካከል የቤተክርስቲያን ደንን መሰረት ያደረገ የመልክዓ-ምድር መልሶ ማልማት ፕሮጀክት አንዱ ነው፡፡ ፕሮጀክቱ በደቡብ ጎንደር ዞን ደራ ወረዳ እና እስቴ ወረዳ እየተተገበረ ይገኛል፡፡ የአመልድ ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር / አለማየሁ ዋሴ የፕሮጀክቱን እንቅስቃሴ በጎበኙበት ወቅት እንዳሉት 100 ዓመታት በፊት 40% የነበረው የደን ሽፋን ወደ 4 በመቶ ዝቅ ብሏል፡፡ በመሆኑም አጭር የዝናብ ወቅት፣ የብዛ-ህይዎት መዛባት እና ለአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭ ሆነናል ብለዋል፡፡

       biodiversity by protecting existing forests  4

ዋና ዳይረክተሩ አክለውም አመልድ ኢትዮጵያ ነባር ደኖችን በመጠበቅ እና አዳዲስ ተከላ በማካሄድ ለብዝሃ-ህይዎት መሻሻል እየሰራን ነው ፡፡ ለአብነትም የቤተ-ክርስቲያን ደኖች ከዚህ በፊት የአንድ ትልቅ ደን አካል የነበሩ በመሆናቸው በተከላ በማጠናከር እና ዙሪያቸውን በድንጋይ በማጠር፣የወል መሬቶች ላይ ተከላ በማካሄድ እና ከእንስሳት ንክኪ ነጻ በማድረግ አንዱን ከአንዱ በማገናኘት የአካባቢ ደህንነትን እና የደን ሽፋንን ለመጨመር እየሰራን ነው ብለዋል፡፡ እንዲሁም ከደን ውጤቶች ጋር ኑሯቸውን የመሰረቱ አርሶ አደሮችን በንብ ማነብ፣ በበግ እርባታ እና በዶሮ እርባታ እንዲሰማሩ በማድረግ የደን ጭፍጨፋን ለመቀነስ እየሰራን ነው ብለዋል፡፡ በተጨማሪም የአካባቢው ወጣቶች ማገዶ ቆጣቢ ምድጃ እንዲያምርቱ እና ለአካባቢው በመተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያቀርቡ ተደርጓል፡፡

      biodiversity by protecting existing forests  3

አመልድ ኢትዮጵያ 2015 . ክረምት በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በሚተገበሩ ፕሮጀክቶች አማካኝነት የአካባቢ ደህንነትን እና የደን ሽፋንን ለመጨመር የሚያግዙ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጥቅም የሚሰጡ 6.8 ሚሊዮን ችግኞች ተከላ እያካሄደ ነው፡፡

      biodiversity by protecting existing forests  2

 


Language Selection
ሶሻል ሚዲያ
FacebookTwitter
የጎብኝዎች ብዛት
Today42
Week218
All139271

Currently are 15 guests online


ምርጫ
ስለ ድረ-ገፅ ያለዎት አስተያየት ?